Accessibility Settings

color options

monochrome muted color dark

reading tools

isolation ruler

ሃብት

የአፍሪካ ዓለማቀፍ የምርመራ ዘገባ ኔትወርክ (GIJN): የሕዝብ መረጃ መዛግብት ተደራሽነት

Read this article in

በሰብ ሰሃራ አፍሪካ በሚገኙ በርካታ አገራት፣ አሁን ድረስ መረጃና የሕዝብ የሆኑ የመረጃ መዛግብትን ማግኘት ፈታኝና ከባድ ሥራ ነው። ለምን ቢባል ጋዜጠኞች መረጃ ሲጠይቁ የሚደግፋቸውና የመንግሥት ባለሥልጣናት የሕዝብ የሆኑ መረጃዎችን እንዲሰጡ ግድ የሚላቸው ሕግ አለመኖሩ ነው።

ሆኖም አንዳንድ አገራት ይህን ጽንፍ ቀይረው መረጃዎች በቀላሉ እንዲገኙ አስችለዋል። የመረጃ አቅርቦትና ተደራሽነትን በሚመለከት የሚመሩበት ሕግ ባለባቸው የሰብ ሰሃራ አፍሪካ አገራት፣ ለጋዜጠኞች የሚጠቅሙና ተመራጭ የሆኑ ምንጮች ከዚህ በታች ተዘርዝረዋል።

የአፍሪካ የመረጃ ነጻነት ማእከል፤ ብቸኛና ቀዳሚ የሆነ መላውን አፍሪካ የሚያዳርሱ የአኅጉሪቱ ምንጮች የሚገኙበት እንዲሁም መረጃዎቹን ተደራሽ ለማድረግ በተወሰነ ሕግ የሚመራ የመረጃ ምንጭ ነው። በአፍሪካም የመረጃ ነጻነት ሕጎች ዙሪያ መረጃዎችን ያቀርባል።

IFEX (ዓለማቀፍ ሐሳብን የመቀያየር ነጻነት) በአፍሪካ የመረጃ ነጻነት ሕጎች እንዲስፋፉ በማድረግ ጥሩ ሂደት ያሳለፈ ሲሆን፣ በትግበራም ያሉና የሚያጋጥሙ ችግሮችን የሚያካትት ነው።

ኬንያ፣ Reporting on Good Governance in Kenya.org የተባለ ድረ ገጽ የመረጃ ተደራሽነትን በሚመለከት ብሔራዊና የክልል ሕግና መመሪያዎችን ሲያብራራ፣ በጋዜጠኞች ልምድ ዙሪያ ዘገባዎችን ለንባብ ያቀርባል። ጥሩ የገጽ ቅንብርም አለው። እዚህ ላይ በካቲባ ኢንስቲትዩት በኬንያ ሕግ ዙሪያ የተዘጋጀ የመመሪያ መጽሐፍ መመልከት ይቻላል።

ላይቤሪያ፣ InfoLib የመረጃ ነጻነት ጥያቄዎችን ለማደራጀት የኦንላይን ዘዴዎችን ያቀርባል። ራሱን ችሎ የሚንቀሳቀስ አገልግሎት ሰጪ ይሁን እንጂ፣ በላይቤሪያ የመረጃ ኮሚሽን ድረገጽ ‹ቴክ አክሽን› በሚል ማስፈንጠሪያ ስርም ይገኛል።

ሞዛምቢክ: Guia do Direito à Informação Para Jornalistas, በዓለማቀፍ ምርምርና ልውውጥ ቦርድ የተዘጋጀ፣ ለጋዜጠኞች የ2016 የመረጃ ነጻነት መመሪያ።

ናይጄሪያR2KNigeria ስለመረጃ ነጻነት ሕጎች ጠቃሚ መረጃዎችን ያቀርባል። የናይጄሪያው ኤክስትራክቲፍ ኢንዱስትሪ ግልጽነትን መነሻ በማድረግ በኢንተርኔት ለኦንላይን አገልግሎት ጥያቄዎች የመረጃ ነጻነት ሕጎችን ፖርታል አካትቷል። የፐብሊክ ሰርቪስ ሪፎርም ቢሮም በተመሳሳይ እነዚህን የመረጃ ነጻነት ሕች ያካተተ ፖርታል አለው። በሚያዝያ 2018 ደግሞ የማኅበረ ኢኮኖሚያዊ መብቶች እና ግዴታዎች ፕሮጀክት አንድ መመሪያ አሳትሟል። ይህም መረጃ የማግኘት መብትን በመጠቀም በጤና ዘርፍ፣ በትምህርት እንዲሁም በውሃ መስክ ያሉ ሙስናዎችን መጋፈጥ የሚል ነው።

ሩዋንዳ: Sobanukirwa ነጻ ገጽ ሲሆን፣ የሚቀርቡ ጥያቄዎችን በኢንግሊዝኛ፣ ኢንያሩዋንዳ እና ፈረንሳይኛ ቋንቋዎች ያደራጃል።

ደቡብ አፍሪካ፡  ‹Open Democracy Advice Centre› የመረጃ ተደራሽነትን ከማስተዋወቅ አንጻር የመረጃ ሰነድ መጠየቂያ ፎርም ያቀርባል፣ ድጋፍም ያደርጋል። Right2Know› የተባለውም በዋናነት ግልጽነትን በመደገፍ የሚሟገት ቡድን ነው።‹ ODAC› በተመሳሳይ የመረጃ ተደራሽነትን ከማስፋፋት አንጻር፣ መረጃ የማግኘት መብት ዙሪያ ድጋፍ ያደርጋል።

የደቡብ አፍሪካ የሚድያ ተቋም፡ በአፍሪካ የመረጃ ነጻነት ሕጎች ሊንክ የሚገኝበት ገጽ ያለው ነው፣

ዮጋንዳ: ‹መንግሥታችሁን ጠይቁ› ዩጋንዳ› (Ask your Gov Uganda) በኦንላይን በሚገኝ የመረጃ ነጻነት መጠየቂያ ፖርታል ሲሆን፣ ተጠቃሚዎች በቀጥታ ለመንግሥት ተቋማት የመረጃ ጥያቄ የሚያቀርቡበት ነው። ድረ ገጹ በይፋ ለእነዛ ጥያቄዎች መልሶችን ይሰጣል።

Republish our articles for free, online or in print, under a Creative Commons license.

Republish this article


Material from GIJN’s website is generally available for republication under a Creative Commons Attribution-NonCommercial 4.0 International license. Images usually are published under a different license, so we advise you to use alternatives or contact us regarding permission. Here are our full terms for republication. You must credit the author, link to the original story, and name GIJN as the first publisher. For any queries or to send us a courtesy republication note, write to hello@gijn.org.

Read Next

የናይጄሪያው ዓለማቀፍ የምርመራ ዘገባ ማእከል (ICIR) በኮቪድ 19 ምላሽ ተጠሪነትን ለመፍጠር እያደረገ ያለው ግፊት

መቀመጫውን በናይጄሪያ ያደረገ ለትርፍ ያተቋቋመው የናይጄሪያ ዓለማቀፍ የምርመራ ዘገባ ማእከል (ICIR)፣ አሁን ላይ ሽፋኑንም አገሪቱ ለኮቪድ 19 እየሰጠች ባለችው ምላሾች ዙሪያ አድርጓል። በዓለማቀፍ የምርመራ ዘገባ ኔትወርክ (GIJN) የአፍሪካ ኤዲተር ከሆነው ከቤኖን ኸርበርት ኦሉካ ጋር ቆይታ ያደረገው ዳዮ አይታን ስለ ቡድኑ እንቅስቃሴ እንዲሁም ለአፍሪካ ስጋት በሆነው ወረርሽኙ ዙሪያ የምርመር ዘገባ መሥራትን በሚመለከት አንስቷል። ዳዮ አይታን የምርመራ ዘጋቢ፣ የዜና ክፍል አማካሪና የሚድያ አሠልጣኝ ነው።